top of page
DSCN0044[1].JPG
DSCN0018[1].JPG
DSCN0039[1].JPG
DSCN0048[1].JPG

የዓለማዉያን ፍራንቺስካውያን (የሶስተኛ ማህበር) የህንፀት፤ የስልጠና እና አውደ ጥናት መርሀ ግብር በብሄራዊ ደረጃ ለአራት ተከታታይ  ቀናት ተደረገ፡፡

ከጥር 6/2013 እስከ ጥር 9/2013 ሲካሄድ በነበረው የስልጠና እና የህንፀጽት መርሀ ግብር ላይ በብሄራዊ ደረጃ ከተለያዩ ቁምስናች እና ከኤርትራ የመጡ የሶስተኛ ማህበር አባል ወንድሞችና እህቶች ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን የመክፈቻ ቅዳሴ በክቡር አባ ገብረወልድ ገብረጻዲቅ በኢትዮጵያ የካፑቺን ፍራንቺስካውያን ማህበር የበላይ ጠባቂ የተደረገ ሲሆን በተለያዩ ርዕሶች ትምህርት፤ ስልጠና፤ ውይይት እና አውደ ጥናት ሊደረግ ችሏል፡፡ በዚህም መርሀ ግብር በብሔራዊ ደረጃ የሚያስተባብሩ ጊዜያዊ መማክርት ጉባኤ የተቋቋመ ሲሆን፤ የመጨረሻ መሀላ ያደረጉ የሶስተኛ ማህበር ወንድሞችና እህቶች መሀላ የማሳደስ ስራ ተሠርቷል፤

በመጨረሻም  ደስ በሚል መልኩ የወንድማማችነትና የእህታማማችነት ጊዜን በማሳለፍ የመዝጊያ ቅዳሴ በብጹ አባታችን አቡነ ሙሴ ገ/ጊዮሪጊስ የእምድብር ሀገረስብከት ጳጳስ ተፈጽመዋል፡፡

DSCN0118[1].JPG
DSCN0039[1].JPG
bottom of page